2016 ዲሴምበር 9, ዓርብ

መሻቴ

መሻቴ እኔን ሽቶ፣
ፍለጋውን ለፍቶ፣
ካለሁበት መጥቶ፡፡

መኖርን ሻትኩና፣
እሱም ተገኘና፣
ፈታ ተባለና፣
ዳግም ተሰልችቶ፣
ሌላ መሻት መጥቶ፣
ደግሞ እሱም ወጥቶ፣
መጥቶ ወጥቶ፣
መጥቶ ወጥቶ …..

ዳግም ልቆ መጥቶ፣
ተገኝቶና ወጥቶ፣
እምነትን ተራራ ልቤ ላይ ገንብቶ፣
ላይመለስ ሄደ ቤቴን ተሰናብቶ፡፡

2016 ሴፕቴምበር 29, ሐሙስ

የበሬው ስጋት

2016 ሴፕቴምበር 6, ማክሰኞ

አሸንዳ

አሸንዳ
የኔ ልጅ አበባ የኔ ነጭ ወረቀት፣
በቴሌቪዥን መስኮት አይታ እንደገባት፣
ቀጤማ አገልድማ የምትጨፍርበት፣
ለአሸንዳ በዓል ባመት አደረሳት፡፡
እኔም በዚሁ መስኮት መረጃ የሰማሁት፣
የከተማው ቧንቧ ውሃ መስጠት ማቃት፣
ያሸንዳን ሌላ ገጽ ስኖር አሳየኋት፡፡
ይሄንን አሸንዳ ቅርስ ነው ያላችሁ፣
የኔን ቤት አሸንዳም አትርሱት ባካችሁ፡፡