2016 ጁን 16, ሐሙስ

አሜን

ግራ ጐኔን ብዬ በምብርክክ ስለምን፣
ልቤንም አግዞት በፍቅር እንዳምን፣
ሲሰጠኝ አውቄ ብያለሁኝ አሜን፡፡
በሳት ተፈትነሽ ነጥረሽ እየወጣሽ፣
ለቤቴ ምሰሶ በቃሉ የሰራሽ፣
የህይወቴን ፋና በፍቅርሽ አበራሽ፡፡
ካንቺ ጋራ መኖር ፍፁም አይሰለችም፣
ቃሌን ተቀበይኝ ያንቺ ነኝ ዘላለም፡፡
አሜን ይሁንልን በበረከት ይሙላን፣
የልጆችን ደስታ ከእድሜ ጋር ያሳየን፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ