2016 ኤፕሪል 28, ሐሙስ

እግሬን ያጠብክ ለት …

የሰማዩ ንጉስ ከዙፋንህ ወርደህ፣
ጭራሽ አጐንብሰህ እኔነቴን ወደህ
የኔን ልብ ለማግኘት ተራራውን ወጥተህ፣
ለሌቱን በሙሉ ስትፀልይ አብዝተህ፣
ከጥልቁ እንቅልፌ አነቃኝ ፀሎትህ፤

ልቤን ያጢያት ድንጋይ ተጭኖበት ኑሮ፣
ከቦታው አስቶ ቁልቁል አሽቀንጥሮ፣
እንደግሮቼ እመሬት ሲተሻሽ ኖሮ፤

እግሬን ያጠብክ ለት ባንድ ታጠበና፣
የክፋትን ሥሩን ጣለው ነቀለና፡፡

2 አስተያየቶች: