2014 ኖቬምበር 5, ረቡዕ

ዝም አሰኘኝ

ፍቅሩንም ለመቅመስ፣
ቃሉን ለማወደስ፣
ለመስማት ሲቀደስ፣
ከፍላጐት ንፋስ፣
አደረገኝ ትንፍስ፡፡

ሃሳቤን ሞላልኝ፣
ሁሉ ተሳካልኝ
ፀሎት አለቀብኝ፣
በፈቃዴ አዋለኝ፡፡
በደስታ ቦርቃ
በምስጋናው ልቃ፣
ልቤን ደስ እያለኝ፣
ብቻ ዝም አሰኘኝ፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ