2016 ዲሴምበር 9, ዓርብ

መሻቴ

መሻቴ እኔን ሽቶ፣
ፍለጋውን ለፍቶ፣
ካለሁበት መጥቶ፡፡

መኖርን ሻትኩና፣
እሱም ተገኘና፣
ፈታ ተባለና፣
ዳግም ተሰልችቶ፣
ሌላ መሻት መጥቶ፣
ደግሞ እሱም ወጥቶ፣
መጥቶ ወጥቶ፣
መጥቶ ወጥቶ …..

ዳግም ልቆ መጥቶ፣
ተገኝቶና ወጥቶ፣
እምነትን ተራራ ልቤ ላይ ገንብቶ፣
ላይመለስ ሄደ ቤቴን ተሰናብቶ፡፡

1 አስተያየት: