2017 ሴፕቴምበር 8, ዓርብ

ፍልስፍና - ዘመድህ አድርገኝ

የዘርዐ ያዕቆብን ፍልስፍና የሚል መጽሐፍ አንብቤ እንደው የነካኝን ማንነቱን የፍቅር መምህርነቱን ከዚህ ትውልድ ጋር እንዲህ አገናዝቤ ከተብኩት፡፡

ዘርዓያዕቆብ ዘረ ስደተኛ፣
እምነት ፍቅር አንሶት ከሆነ ጦረኛ፣
ዘመዶችህን ተውህ ለክፋት ላትተኛ፤
በዋሻ ተደበቅህ ክፉ ቀን እስኪያልፍ፣
ብዙ ኑሮህን ኖርህ በፈጣሪ እቅፍ፡፡

           ጵጵስና ታጨተህ በዋሻ ውስጥ ብትቆይ፣
           ቤተስቲያን ልትኖር የግዚአብሔር አገልጋይ፣
           መቼ አወቁልህ በሰው ናፍቆት ብትጋይ፣
           ነገርን ለመሸሽ ከመንጋው ብትለይ፣
           ከጥላቻ እንጂ ከሰው እንዳትለይ፡፡

 ደግሞም የተጠጋህ ከሃብቱ በሥራ፣
 ለኑሮ የሚበቃ መሆን መረጥህ ተራ፣
 የሃብቱን ደግነት እጅጉን መረጥኸው፣
 የሚልቅን ዋጋ ዝምድናን ጠየቅኸው፡፡
በሃብቱ ዝምድናም እጅጉን ተባረክህ፣
ጐረቤቱም ሆነህ ፍቅር ቤትህን ሰራህ
ዘመዶችህንም በፍቅር ተሰናበትህ፡፡

      ያንተ አርዓያ ዘሩ በርክቶ በዛና፣
      ሁሉም ዘመዶቹን እጅጉን ተወና፣
     ስደትን መረጠ እርቆ ወጣና፡፡

እድሉን ቢሰጠው ሰርቶ እንዲበላ፣
እየተዘመደ ባለም ሁሉ መላ፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ