2014 ሴፕቴምበር 2, ማክሰኞ

ግማሽ ጨረቃ


ግማሽ ነች ጨረቃ ዛሬ የተባልሽው፣
ባለፈው ሰሞን ግን ሙሉ የነበርሽው
ምን ቆረሰሽ ከጐን ምንስ አጐደለሽ?
ወይስ ሙሉነትሽን ማነው የደበቀሽ?

ፀሀይ ሙቀትሽን ስትታጠን አድራ፣
አስባ ተውባ እጅጉንም አምራ፣
ማልዳ ትወጣለች ለአለም ልታበራ፡፡

ጨረቃ ድምቡልቃ ሰው ከተኛ ወጥተሽ፣
ለሱም ኃፍረት ይዞሽ በግማሽ ጐን ወጣሽ፡፡

ፀሀይም ጐንሽን በከፊል ደብቃ
ግማሽ ስትወጪ ማነስሽን ንቃ፣
ሲነጋላት ደግሞ እንድትታይ ልቃ፡፡

ጨረቃ ሙሉ ነሽ ውበትሽ ደማቅ፣
እንቅልፍ ለማይጥለው አንቺን ለሚያውቅ፣
የነፍስ ምግብ ነሽ ሁል ጊዜም ብርቅ፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ