2014 ፌብሩዋሪ 24, ሰኞ

ውሃን ለፍቅር

የአባይ ተፋሰስ ውሃ ተጣጪዎች፣
ባንድ የተጋበዙ የግዜር ታዳሚዎች፣
ውሃ ከሰማይ ላይ መሆኑን ተረድተን፣
ትብብር ላይ ሆነን አብረን እየሰራን
ተስማምተን ልንጠጣ ባንድ ከተሰጠን፣
በቅናት ነደደ ፍቅር ጠላ ሰይጣን፡፡

ስስትን ዘራና በግብጽ ጋዜጦች፣
ቁጣን ጨመረና በግብፅ የሰው ልቦች፣
መገፋፋት መጣ ወደኃላ ማለት፣
ጠልተውንም ሳይሆን ብቻ ለራስ ማድላት፡፡

የጥል መሠረቱ ነውና ዲያቢሎስ፣
የልቡ አምሮቱ እንድንጨራረስ፡፡
ስልጣኑም ተሰጥቶት ሊፈትን ከጌታ፣
ያናፍስብናል የስስት ጫጫታ፡፡

ቸግሮት አይደለም የሰጠን ባንድ ላይ
እንድንኖር ሽቶ ነው እንዲህ ሳንለያይ፣
ከሰይጣን እንድንበልጥ በደንብ እናውቃለን፣
ለትብብር ለፍቅር እንበረታለን፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ