ግራ ጐኔን ብዬ በምብርክክ ስለምን፣
ሲሰጠኝ አውቄ ብያለሁኝ አሜን፡፡
በሳት ተፈትነሽ ነጥረሽ እየወጣሽ፣
የህይወቴን ፋና በፍቅርሽ አበራሽ፡፡
ካንቺ ጋራ መኖር ፍፁም አይሰለችም፣
ቃሌን ተቀበይኝ ያንቺ ነኝ ዘላለም፡፡
አሜን ይሁንልን በበረከት ይሙላን፣
የልጆችን ደስታ ከእድሜ ጋር ያሳየን፡፡
የሰማዩ ንጉስ ከዙፋንህ ወርደህ፣
የኔን ልብ ለማግኘት ተራራውን ወጥተህ፣
ለሌቱን በሙሉ ስትፀልይ አብዝተህ፣
ከጥልቁ እንቅልፌ አነቃኝ ፀሎትህ፤
ልቤን ያጢያት ድንጋይ ተጭኖበት ኑሮ፣
ከቦታው አስቶ ቁልቁል አሽቀንጥሮ፣
እንደግሮቼ እመሬት ሲተሻሽ ኖሮ፤
የክፋትን ሥሩን ጣለው ነቀለና፡፡